7 /ሰባት/ የከፍተኛ ፍ/ቤቱ የሥራ ሂደቶች በፋግታ ወረዳ የ2 ቀን ስልጠና ሰጡ ፡-
በፍርድ ቤቶች ያለውን የአሰራር ክፍተት ለመሙላት ከወረዳ ፍርድ ቤት እስከ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያለውን የአሰራር አንድ ለማድረግ የ2 ቀን ስልጠና በፋግታ ለኮማ ወረዳ ፍ/ቤት ከጥቅምት 18-19/2ዐዐ4 ዓ/ም ድረስ ስልጠና የተሰጠ ሲሆን፣ በስልጠናው የተሣተፉ ብዛት ወንድ 58 ሴት 46 ድምሩ 1ዐ4 ሰራተኞች ስልጠናውን ወስደዋል፡፡
እነሱም በስልጠናው የተሳተፉ ሂደቶች ፡-
የሰው ኃይል ደጋፊ የሥራ ሂደት፣ የወንጀል እና የፍታብሔር ዋና የሥራ ሂደት፣የህዝብ ግንኙነት ደጋፊ የሥራ ሂደት፣ የውጥ ኦዲት ደጋፊ የሥራ ሂደት፣ የቅሬታ ሰሚ ደጋፊ የሥራ ሂደት፣ የICT ደጋፊ የሥራ ሂደት ናቸው፡፡
የመክፈቻ ንግግር በማድረግ የስልጠናውን መጀመር ያበሰሩት የሰው ኃይል ደጋፊ የሥራ ሂደት አስተባባሪ የሆኑት አቶ አስፋው ይታየው እንደተናገሩት በዚህ አጭር ቀን ውስጥ በቂ የሆነ ስልጠና ይሰጣችኋል ባይባልም ሥራ በምትሰሩበት ጊዜ የሚያጋጥማችሁን ችግር ጭምር በማንሣት እንድትወያዩ በማለት አሳስበው ሁሉም ሂደቶች ወደተዘጋጀላቸው የስልጠና ቦታ ተንቀሳቅሰው አንድ ቀን ተኩል /1/2 በተናጠል ስልጠናውን ከወሰዱበኋላ የግማሽ ቀን የጋራ ውይይት ተደርጐ ለከፍተኛ ፍርድ ቤቱ የሚቀርቡ የተለያዩ ጥያቄዎችን በማንሣት እና በተነሱትም ጥያቄዎች ላይ ምላሽ በተሰጥቶባቸው በኋላ የከፍተኛ ፍርድ ቤት ኘሬዚዳንት በተወካያቸው በኩል የተላከውን የመዝጊያ ንግግር በማድረግ በተሣካ ሁኔታ ስልጠናው ተጠናቋል፡፡ |